by Tibebe Belay on Thursday, May 17, 2012 at 10:42am ·
ጊዜው
በአገራችን ኢትዮጵያ የመንግሥት ለውጥ የተደረገበት ወቅት ነው። መቼም በዘመናችን የሚገኙ የአፍሪካ ‘ነገሥታት’
(ከአንዱ በስተቀር) የሚታወቁት፤ የቀደሙትን ማለትም የተኩዋቸውን ‘ነገሥታት’ መልካም ሥራ ሳይሆን የፈጸሙትን
በደልና ግፍ፣…. ገመናቸውን ሁሉ ጉድጉዋድ ቆፍረው፣ ፋይል በርብረው… ወደ ብርሐን እያወጡ በበደለኝነት በመክሰስና
እነርሱ ግን በነዚህ “ግፈኞች” ነውር ላይገኙ ተስፋ በመስጠት ነውና፤ በእኛም አገር ይኸው ታሪክ የተደገመበት ጊዜ
ነበር። 1983-84።
በወቅቱ “የቀይ ሽብር ወንጀለኞች” የሚል ስም የተሰጣቸው የደርግ ባለስልጣናትና “የበታች ሹመኞች” ከያሉብት ታድነው፣ በየኣካባቢው በሚገኙ የቀበሌ አዳራሾች፣ በየበደሉት ሕዝብ ፊት እየቀረቡ “አውጫጭኝ” ይካሄድ ነበር። እኔም ይሄንኑ ‘ስርዓት’ ለመከታተል ቦሌ አካባቢ በሚገኘውና ዛሬ “ሻላ” ተብሎ በሚጠራው አዳራሽ ውስጥ ተገኝቼአለሁ። በኣዳራሹ ግድግዳ ላይ “የቀይ ሽብር ሰለባዎች” ናቸው የተባሉ ወጣቶች ፎቶ ተሰቅሎአል። በመድረኩም ላይ ‘ወንጀለኞቹ’ ለሕዝብ እይታ ቀርበዋል። በአዳራሹ ውስጥ የነበረው ድባብ እጅግ ያስፈራል። ልጆቻቸውን በከፍተኛ ድብደባና ጥይት ያጡ ወላጆች እየተነሱ ይህንን ግፍ በፈጸሙት ‘ወንጀለኞች’ ላይ ጣቶቻቸውን እየጠቆሙና ድምጻቸውን ከፍ እያደረጉ የቻሉትን ያህል የቁጣና የስድብ ውርጅብኝ ያወርዱባቸዋል። ‘ወንጀለኞቹም’ አንገታቸውን ሰብረው አይናቸውን እያቁለጨለጩ ውርጅብኙን ‘በጸጋ’ ይቀበላሉ።
ይሄ ‘ትይንት’ ለረጅም ሰዓታት ቀጥሎአል። በዚህ ግርግር መሀል በድንገት አንድ አዛውንት ተነስተው የወጣቶቹ ፎቶ ተሰቅሎ ወደነበረበት ግድግዳ አመሩ። ከፎቶዎቹም መሀል አንዱን አንስተው ‘ወንጀለኞቹ’ ወደተቀመጡበት መድረክ ቀረቡ። ፊታቸውንም ወደሕዝቡ አዙረው እጅግ ልብ በሚሰብር ሁኔታ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ። በአዳራሹ መሀል የሚገኝ አንድ ወጣትም በተለየ ሁኔታ አብሮአቸው ያለቅስ ነበር። ከረጅም ደቂቃዎች በህዋላ አዛውንቱ በተቻላቸው መጠን ራሳቸውን ገዝተው ሲያበቁ፣ በከፍተኛ ድምጽ “እግዚአብሔር ይመስገን!!” ብለው ጮሁ። የአዳራሹ ሁካታ ጥይት የተተኮሰ ያህል በከፍተኛ ዝምታ ተሞላ። “እግዚአብሔር ይመስገን!!” አሉ በድጋሚ። “አባታችን ሆይ የሚለውን ጸሎት መጸለይ ካቆምኩ አስራ ሰባት ዓመቴ።” በመድረኩ ላይ የተኮለኮሉት ‘ምስኪኖችም’፣ ‘ጠላቶቹን’ በቁጣና በስድብ ለመበቀልም ሆነ እንደእኔ በዚህ “የበቀል መድረክ” ላይ የሚከናወነውን ስርዐት ለመከታተል አዳራሹን የሞላው ሕዝብ አፉን ከፍቶ፣ ዓይኑን አፍጥጦ ከኣዛውንቱ የሚወጣውን ቃል በአንክሮ መከታተል ጀመረ። አዛውንቱ ቀጠሉ፡-
“አባታችን ሆይ የሚለውን ጸሎት መጸለይ ካቆምኩ ይኸው ድፍን አስራ ሰባት ዓመቴ። በዚህ ጸሎት ውስጥ ‘እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል፣ በደላችንን ይቅር በለን’ የሚል ቃል አለ። ታድያ እኔ የልጄን ገዳይ ይቅር ሳልል እንዴት አፌን ሞልቼ እግዚአብሔርን በደሌን ይቅር በለኝ ልበለው??? እግዚአብሔር ይመስገን!!! ከዛሬ ጀምሮ አምላኬን በደሌን ይቅር በለኝ እለዋለሁ። እግዚአብሔር አምላኬ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ እኔን በደለኛውን ይቅር እንዳለኝ፣ ይኸው ዛሬ የልጄን ገዳይ ይቅር አልኩት፣” አሉና በመድረኩ ላይ ከተኮለኮሉት ሰዎች መሀል አንዱን እቅፍ አድርገው ሳሙት። እጅግ በጣም የሚደንቀው ነገር፣ እኒህ አዛውንት በይቅርታ የሳሙት ሰው በቤታቸው ውስጥ እንጀራቸውን የበላ፣ በችግሩ የደረሱለት… ‘የቅርብ ሰው’ መሆኑ ነው።
በኣዳራሹ ውስጥ ነግሶ የነበረው የበቀልና የቁጣ መንፈስ ለጥቂት ደቂቃዎች ገሸሽ አለ። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ያ አዛውንቱ ሲያለቅሱ በተለየ ሁኔታ አብሮአቸው ሲያለቅስ የነበረ ወጣት በከፍተኛ ቁጣና ንዴት፡- “አይሆንም አባዬ!! እኔ የአንዱን ወንድሜን ገዳይ በሕግ እበቀለዋለሁ…” እያለ በመጮህ “ለያዥ ለገናዥ” አስቸገረ። አባትየው በብዙ ለመኑት። እርሱ ግን “የሕግ ሰው” በመሆኑ የወንድሙን ገዳይ በሕግ እንደሚፋረደው አጥብቆ ተናገረ።
ጥቂት ዓመታት አለፉ፤ የወንድሙን ገዳይ በሕግ እንደሚፋረደው የተናገረው ወጣት በድንገተኛ ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። አሁንም ጥቂት ዓመታት አለፉ፤ እኒያ አዛውንት ሌሎች የምሕረት ዓመታት ተጨምረውላቸውና ዕድሜ ጠግበው በደላቸውን ይቅር ካላቸው ጌታ ጋር ተገናኙ። እንደገና ጥቂት ዓመታት አለፉ፣ በነፍስ ግድያ የተወነጀለው ሰው የፍርዱን ጊዜ በሚጠባበቅበት ወህኒ ውስጥ ጌታ አገኘው። መቼስ ወህኒ ቤት ሰዎች የተለያየ ‘እውቀት’ እየቀሰሙ የሚወጡበት ትምሕርት ቤት ነውና ይሄም ሰው የፍርድ ጊዜውን አጠናቆ ከወህኒ ሲወጣ እዚያው ቦሌ አካባቢ ከሚገኝ አንድ የወንጌላውያን ቤተ ክርሰቲያን ውስጥ የበረታ አገልጋይ ሆነ።
“እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፡- በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ! ስምህ ይቀደስ፣ መንግሥትህ ትምጣ፣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፣ የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፣ እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፣ ከክፉም አድነን እንጂ ወደፈተና አታግባን፣ መንግሥት የአንተ ናትና ኃይልም ክብርም ለዘለዓለሙ አሜን። ለሰዎች ኃጢኣታቸውን ይቅር ብትሉ፣ የሰማዩ ኣባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችሁዋልና፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፣ አባታችሁም ኃጢኣታችሁን ይቅር አይላችሁም።” (ማቴ.6፡9-15)
በወቅቱ “የቀይ ሽብር ወንጀለኞች” የሚል ስም የተሰጣቸው የደርግ ባለስልጣናትና “የበታች ሹመኞች” ከያሉብት ታድነው፣ በየኣካባቢው በሚገኙ የቀበሌ አዳራሾች፣ በየበደሉት ሕዝብ ፊት እየቀረቡ “አውጫጭኝ” ይካሄድ ነበር። እኔም ይሄንኑ ‘ስርዓት’ ለመከታተል ቦሌ አካባቢ በሚገኘውና ዛሬ “ሻላ” ተብሎ በሚጠራው አዳራሽ ውስጥ ተገኝቼአለሁ። በኣዳራሹ ግድግዳ ላይ “የቀይ ሽብር ሰለባዎች” ናቸው የተባሉ ወጣቶች ፎቶ ተሰቅሎአል። በመድረኩም ላይ ‘ወንጀለኞቹ’ ለሕዝብ እይታ ቀርበዋል። በአዳራሹ ውስጥ የነበረው ድባብ እጅግ ያስፈራል። ልጆቻቸውን በከፍተኛ ድብደባና ጥይት ያጡ ወላጆች እየተነሱ ይህንን ግፍ በፈጸሙት ‘ወንጀለኞች’ ላይ ጣቶቻቸውን እየጠቆሙና ድምጻቸውን ከፍ እያደረጉ የቻሉትን ያህል የቁጣና የስድብ ውርጅብኝ ያወርዱባቸዋል። ‘ወንጀለኞቹም’ አንገታቸውን ሰብረው አይናቸውን እያቁለጨለጩ ውርጅብኙን ‘በጸጋ’ ይቀበላሉ።
ይሄ ‘ትይንት’ ለረጅም ሰዓታት ቀጥሎአል። በዚህ ግርግር መሀል በድንገት አንድ አዛውንት ተነስተው የወጣቶቹ ፎቶ ተሰቅሎ ወደነበረበት ግድግዳ አመሩ። ከፎቶዎቹም መሀል አንዱን አንስተው ‘ወንጀለኞቹ’ ወደተቀመጡበት መድረክ ቀረቡ። ፊታቸውንም ወደሕዝቡ አዙረው እጅግ ልብ በሚሰብር ሁኔታ ስቅስቅ ብለው አለቀሱ። በአዳራሹ መሀል የሚገኝ አንድ ወጣትም በተለየ ሁኔታ አብሮአቸው ያለቅስ ነበር። ከረጅም ደቂቃዎች በህዋላ አዛውንቱ በተቻላቸው መጠን ራሳቸውን ገዝተው ሲያበቁ፣ በከፍተኛ ድምጽ “እግዚአብሔር ይመስገን!!” ብለው ጮሁ። የአዳራሹ ሁካታ ጥይት የተተኮሰ ያህል በከፍተኛ ዝምታ ተሞላ። “እግዚአብሔር ይመስገን!!” አሉ በድጋሚ። “አባታችን ሆይ የሚለውን ጸሎት መጸለይ ካቆምኩ አስራ ሰባት ዓመቴ።” በመድረኩ ላይ የተኮለኮሉት ‘ምስኪኖችም’፣ ‘ጠላቶቹን’ በቁጣና በስድብ ለመበቀልም ሆነ እንደእኔ በዚህ “የበቀል መድረክ” ላይ የሚከናወነውን ስርዐት ለመከታተል አዳራሹን የሞላው ሕዝብ አፉን ከፍቶ፣ ዓይኑን አፍጥጦ ከኣዛውንቱ የሚወጣውን ቃል በአንክሮ መከታተል ጀመረ። አዛውንቱ ቀጠሉ፡-
“አባታችን ሆይ የሚለውን ጸሎት መጸለይ ካቆምኩ ይኸው ድፍን አስራ ሰባት ዓመቴ። በዚህ ጸሎት ውስጥ ‘እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል፣ በደላችንን ይቅር በለን’ የሚል ቃል አለ። ታድያ እኔ የልጄን ገዳይ ይቅር ሳልል እንዴት አፌን ሞልቼ እግዚአብሔርን በደሌን ይቅር በለኝ ልበለው??? እግዚአብሔር ይመስገን!!! ከዛሬ ጀምሮ አምላኬን በደሌን ይቅር በለኝ እለዋለሁ። እግዚአብሔር አምላኬ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ እኔን በደለኛውን ይቅር እንዳለኝ፣ ይኸው ዛሬ የልጄን ገዳይ ይቅር አልኩት፣” አሉና በመድረኩ ላይ ከተኮለኮሉት ሰዎች መሀል አንዱን እቅፍ አድርገው ሳሙት። እጅግ በጣም የሚደንቀው ነገር፣ እኒህ አዛውንት በይቅርታ የሳሙት ሰው በቤታቸው ውስጥ እንጀራቸውን የበላ፣ በችግሩ የደረሱለት… ‘የቅርብ ሰው’ መሆኑ ነው።
በኣዳራሹ ውስጥ ነግሶ የነበረው የበቀልና የቁጣ መንፈስ ለጥቂት ደቂቃዎች ገሸሽ አለ። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ያ አዛውንቱ ሲያለቅሱ በተለየ ሁኔታ አብሮአቸው ሲያለቅስ የነበረ ወጣት በከፍተኛ ቁጣና ንዴት፡- “አይሆንም አባዬ!! እኔ የአንዱን ወንድሜን ገዳይ በሕግ እበቀለዋለሁ…” እያለ በመጮህ “ለያዥ ለገናዥ” አስቸገረ። አባትየው በብዙ ለመኑት። እርሱ ግን “የሕግ ሰው” በመሆኑ የወንድሙን ገዳይ በሕግ እንደሚፋረደው አጥብቆ ተናገረ።
ጥቂት ዓመታት አለፉ፤ የወንድሙን ገዳይ በሕግ እንደሚፋረደው የተናገረው ወጣት በድንገተኛ ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ። አሁንም ጥቂት ዓመታት አለፉ፤ እኒያ አዛውንት ሌሎች የምሕረት ዓመታት ተጨምረውላቸውና ዕድሜ ጠግበው በደላቸውን ይቅር ካላቸው ጌታ ጋር ተገናኙ። እንደገና ጥቂት ዓመታት አለፉ፣ በነፍስ ግድያ የተወነጀለው ሰው የፍርዱን ጊዜ በሚጠባበቅበት ወህኒ ውስጥ ጌታ አገኘው። መቼስ ወህኒ ቤት ሰዎች የተለያየ ‘እውቀት’ እየቀሰሙ የሚወጡበት ትምሕርት ቤት ነውና ይሄም ሰው የፍርድ ጊዜውን አጠናቆ ከወህኒ ሲወጣ እዚያው ቦሌ አካባቢ ከሚገኝ አንድ የወንጌላውያን ቤተ ክርሰቲያን ውስጥ የበረታ አገልጋይ ሆነ።
“እንግዲህ እናንተስ እንዲህ ጸልዩ፡- በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ! ስምህ ይቀደስ፣ መንግሥትህ ትምጣ፣ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን፣ የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን፣ እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፣ ከክፉም አድነን እንጂ ወደፈተና አታግባን፣ መንግሥት የአንተ ናትና ኃይልም ክብርም ለዘለዓለሙ አሜን። ለሰዎች ኃጢኣታቸውን ይቅር ብትሉ፣ የሰማዩ ኣባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችሁዋልና፤ ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፣ አባታችሁም ኃጢኣታችሁን ይቅር አይላችሁም።” (ማቴ.6፡9-15)
No comments:
Post a Comment