1. ልጅነት
"ልጆች ሆይ ኃጢአታችሁ ስለ ስሙ ተሰርዮላችኋልና እጽፍላችኋለሁ" 1ዮሓ 2:12
በክርስቶስ በማመን ዳግመግኛ በምንወለድበት ጊዜ ጴጥሮስ እንዳለው "አሁን እንደተወለዱ ሕጻናት" ነን:: ተፈጥሮአዊ ልደታችንም እንደሚያስተምረን ለማደግም ሆነ አካባቢያችንን ለመለማመድ ጊዜ ይወስድብናል:: ወላጆቻችን በሚሰጡን ፍቅርና እንክብካቤ ቀስ በቀስ ዙሪያ ገባችንን እያየን አካባቢያችንን ማወቅና ሁኔታዎችን መለማመድ እንጀምራለን:: በዚህ ጊዜ ውስጥ የተለያዩ ጥፋቶችን ብናደርግ, ለምሳሌ መኝታችን ላይ "ተፈጥሮአዊ ግዴታችንን" ብንፈጽም, ወይም ለመራመድ ስንሞክር ብንወድቅ የሚቆጣን ወይም ሊቀጣን አለንጋ የሚያነሳ ወላጅ ጤነኛ አይደለም:: በልጅነታችን የምንፈጽማቸው ጥፋቶች ሁሉ ያለ እውቀት የሚፈጸሙ ብቻ ሳይሆኑ ወደላይ የሚያሳድጉን መሰላለሎቻችን ናቸው:: ለዚህም ነው ለሕጻናት ከፍቅርና ከእንክብካቤ ምግባቸውንም በየጊዜው ከመመገብ በቀር ቁጣም ሆነ ቁንጥጫ የማይስማማቸው::
ከእግዚአብሔር ዘንድ እውነተኛ የመጋቢነትን አደራ የተቀበሉ አገልጋዮች, በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ አዲስ የተወለዱ መንፈሳዊ ሕጻናትን የሚመግቡበት ጥበብ አላቸው:: ለነዚህ ሕጻናት መሰረታዊ የተባሉትንንና በወተት የተመሰሉትን መንፈሳዊ ምግቦች ከማዘጋጀት በተጨማሪ ምናልባት በሕይወት አካሄዳቸው ላይ የሚከሰተውን የትኛውም አይነት ድካም እንዴት አድርገው መሸከም እንዳለባቸው ያውቁታል:: በተለይም እነዚህ መንፈሳዊ ሕጻናት በሕይወታቸው ላይ በሚያዩት ድካም ተስፋ እንዳይቆርጡና በኃጢአት እንዳይከሰሱ ስለኃጢአታቸው የተከፈለውን ዋጋ ማሳየትና እንደ ሓዋርያው ዮሓንስ "ልጆች ሆይ ኃጢአትን እንዳታድርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ:: ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: እርሱም የኃጢአታችን ማስተሰረያ ነው::" (1ዮሓ 2:1) እያሉ ዘወትር ማነቃቃትና ማበረታታት ይጠበቅባቸዋል:: ዛሬ በብዙ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ያለው ችግር, ሕጻናት - ሕጻናት እንዲሆኑ ጊዜ አይሰጣቸውም:: ትናንት ያጠመቁትን መንፈሳዊ ሕጻን ዛሬ "ሽንቱን ሲሸና" ቢያገኙት ሙልጭ አድርገው ይገርፉታል, (በቃሉ አለንጋ)::
ልጅ ሳለን እንደ ልጅ ማሰባችን, እንደ ልጅ መናገራችንና እንደልጅ መቁጠራችን ጤነኛ ነው:: በልጅ ሃሳብ የሚፈርድ ሰው ግን ጤነኛ አይደለም:: ሕጻናት ቃላትን ከአፋቸው ለማውጣት, አረፍተ ነገር ለመስራትና ሃሳባቸውን ለመግለጥ የሚያደርጉት መፍጨርጨር የማያስቀውና በዚህ የማይደሰት ወላጅ የለም:: ከአልጋ ወርዶ ለመዳህ, ወንበር ተድግፎ ለመቆም, ቆሞም በትክክል ለመራመድ... የሚያደርጉት ጥረት እንዴት ደስ ያሰኛል!!! ደግሞም ሁልጊዜ እየተኮላተፉና ዳዴ እያሉ እንዲኖሩም የሚመኝ አባት አይኖርም:: ሁሉም ወላጅ ልጆቹን ወደ ት/ቤት የሚልከው ልጆቹ በትክክል መናገርና ማሰብ ሲጀምሩሩ ለማየት ከመጓጓት ነው:: ነገር ግን በዚህ ጊዜ በየትኛውም የሕይወት እንቅስቃሴአቸው አቅጣጫ ለሚመጣው ችግር የሕጻናቱ ዋስትና የወላጆችቻቸው ፍቅርና እንክብካቤ ነው::
በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ በመንፈሳዊ እግሮቻችን ቆመንና መንፈሳዊውን ጉዞ ራሳችንን ችለን መጓዝ እስኪሆንልን ድረስ የሚያበረታንና የሚያሳድገን ከየአጥቢያ ቤተክርስቲያኖቻችን የምናገኘው መንፈሳዊ አገልግሎት ነው:: በተለይ - በተለይ, ካለማደጋችን የተነሳ በሕይወታችን ላይ በምናየው ድካም በኃጢአት እንዳንወቀስ ስለበደላችንና ስለኃጢአታችን የፈሰሰውን የልጁን የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እለት - እለት እንድናስብ የሚያግዙን መጽሓፍ ቅዱሳዊ ትምሕርቶችና መንፈሳዊ ዝማሬዎች, በጠላት ዲያብሎስ እንዳንከሰስ የሚረዱን ዋንኛ መሳሪያዎቻችን ናቸው:: በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ስንወድቅ የሚያነሳን ዘላለማዊው የእግዚአብሔር ምሕረት የቆመው, በቀራንዮ መስቀል ላይ በተገለጠው የእግዚአብሔር ፍቅርና ልጁ በከፈለው ዋጋ ላይ ነው:: በየዕለቱ ከእግዚአብሔር ዘንዽ ለምናገኘው ይቅርታና ምሕረት ዋስትናችን በአብ ዘንድ ያለን ጠበቃ ነው::
ዛሬ ብዙዎች በድካማቸው የሚወቀሱትና ደግሞም መፍትሄ ፍለጋ በተለያዩና መጽሓፍ ቅዱሳዊ ባልሆኑ መንገዶች የሚንከራተቱት ስለኃጢአታቸውና ስለድካማቸው የተከፈለውን ይህንን የከበረ ዋጋ በትክክል የሚያሳያቸው እረኛ በማጣታቸው ነው:: ዛሬም ለእነዚህ ወንድሞቻችንና እሕቶቻችን የእግዚአብሔር መንፈስ ያለው ሓዋርያዊ መልእክት "ልጆች ሆይ ኃጢአትን እንዳታድርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ:: ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: እርሱም የኃጢአታችን ማስተሰረያ ነው::" የሚለው ነው:: (የሚቀጥል)
"ልጆች ሆይ ኃጢአታችሁ ስለ ስሙ ተሰርዮላችኋልና እጽፍላችኋለሁ" 1ዮሓ 2:12
በክርስቶስ በማመን ዳግመግኛ በምንወለድበት ጊዜ ጴጥሮስ እንዳለው "አሁን እንደተወለዱ ሕጻናት" ነን:: ተፈጥሮአዊ ልደታችንም እንደሚያስተምረን ለማደግም ሆነ አካባቢያችንን ለመለማመድ ጊዜ ይወስድብናል:: ወላጆቻችን በሚሰጡን ፍቅርና እንክብካቤ ቀስ በቀስ ዙሪያ ገባችንን እያየን አካባቢያችንን ማወቅና ሁኔታዎችን መለማመድ እንጀምራለን:: በዚህ ጊዜ ውስጥ የተለያዩ ጥፋቶችን ብናደርግ, ለምሳሌ መኝታችን ላይ "ተፈጥሮአዊ ግዴታችንን" ብንፈጽም, ወይም ለመራመድ ስንሞክር ብንወድቅ የሚቆጣን ወይም ሊቀጣን አለንጋ የሚያነሳ ወላጅ ጤነኛ አይደለም:: በልጅነታችን የምንፈጽማቸው ጥፋቶች ሁሉ ያለ እውቀት የሚፈጸሙ ብቻ ሳይሆኑ ወደላይ የሚያሳድጉን መሰላለሎቻችን ናቸው:: ለዚህም ነው ለሕጻናት ከፍቅርና ከእንክብካቤ ምግባቸውንም በየጊዜው ከመመገብ በቀር ቁጣም ሆነ ቁንጥጫ የማይስማማቸው::
ከእግዚአብሔር ዘንድ እውነተኛ የመጋቢነትን አደራ የተቀበሉ አገልጋዮች, በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ አዲስ የተወለዱ መንፈሳዊ ሕጻናትን የሚመግቡበት ጥበብ አላቸው:: ለነዚህ ሕጻናት መሰረታዊ የተባሉትንንና በወተት የተመሰሉትን መንፈሳዊ ምግቦች ከማዘጋጀት በተጨማሪ ምናልባት በሕይወት አካሄዳቸው ላይ የሚከሰተውን የትኛውም አይነት ድካም እንዴት አድርገው መሸከም እንዳለባቸው ያውቁታል:: በተለይም እነዚህ መንፈሳዊ ሕጻናት በሕይወታቸው ላይ በሚያዩት ድካም ተስፋ እንዳይቆርጡና በኃጢአት እንዳይከሰሱ ስለኃጢአታቸው የተከፈለውን ዋጋ ማሳየትና እንደ ሓዋርያው ዮሓንስ "ልጆች ሆይ ኃጢአትን እንዳታድርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ:: ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: እርሱም የኃጢአታችን ማስተሰረያ ነው::" (1ዮሓ 2:1) እያሉ ዘወትር ማነቃቃትና ማበረታታት ይጠበቅባቸዋል:: ዛሬ በብዙ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ያለው ችግር, ሕጻናት - ሕጻናት እንዲሆኑ ጊዜ አይሰጣቸውም:: ትናንት ያጠመቁትን መንፈሳዊ ሕጻን ዛሬ "ሽንቱን ሲሸና" ቢያገኙት ሙልጭ አድርገው ይገርፉታል, (በቃሉ አለንጋ)::
ልጅ ሳለን እንደ ልጅ ማሰባችን, እንደ ልጅ መናገራችንና እንደልጅ መቁጠራችን ጤነኛ ነው:: በልጅ ሃሳብ የሚፈርድ ሰው ግን ጤነኛ አይደለም:: ሕጻናት ቃላትን ከአፋቸው ለማውጣት, አረፍተ ነገር ለመስራትና ሃሳባቸውን ለመግለጥ የሚያደርጉት መፍጨርጨር የማያስቀውና በዚህ የማይደሰት ወላጅ የለም:: ከአልጋ ወርዶ ለመዳህ, ወንበር ተድግፎ ለመቆም, ቆሞም በትክክል ለመራመድ... የሚያደርጉት ጥረት እንዴት ደስ ያሰኛል!!! ደግሞም ሁልጊዜ እየተኮላተፉና ዳዴ እያሉ እንዲኖሩም የሚመኝ አባት አይኖርም:: ሁሉም ወላጅ ልጆቹን ወደ ት/ቤት የሚልከው ልጆቹ በትክክል መናገርና ማሰብ ሲጀምሩሩ ለማየት ከመጓጓት ነው:: ነገር ግን በዚህ ጊዜ በየትኛውም የሕይወት እንቅስቃሴአቸው አቅጣጫ ለሚመጣው ችግር የሕጻናቱ ዋስትና የወላጆችቻቸው ፍቅርና እንክብካቤ ነው::
በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ በመንፈሳዊ እግሮቻችን ቆመንና መንፈሳዊውን ጉዞ ራሳችንን ችለን መጓዝ እስኪሆንልን ድረስ የሚያበረታንና የሚያሳድገን ከየአጥቢያ ቤተክርስቲያኖቻችን የምናገኘው መንፈሳዊ አገልግሎት ነው:: በተለይ - በተለይ, ካለማደጋችን የተነሳ በሕይወታችን ላይ በምናየው ድካም በኃጢአት እንዳንወቀስ ስለበደላችንና ስለኃጢአታችን የፈሰሰውን የልጁን የኢየሱስ ክርስቶስ ደም እለት - እለት እንድናስብ የሚያግዙን መጽሓፍ ቅዱሳዊ ትምሕርቶችና መንፈሳዊ ዝማሬዎች, በጠላት ዲያብሎስ እንዳንከሰስ የሚረዱን ዋንኛ መሳሪያዎቻችን ናቸው:: በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ስንወድቅ የሚያነሳን ዘላለማዊው የእግዚአብሔር ምሕረት የቆመው, በቀራንዮ መስቀል ላይ በተገለጠው የእግዚአብሔር ፍቅርና ልጁ በከፈለው ዋጋ ላይ ነው:: በየዕለቱ ከእግዚአብሔር ዘንዽ ለምናገኘው ይቅርታና ምሕረት ዋስትናችን በአብ ዘንድ ያለን ጠበቃ ነው::
ዛሬ ብዙዎች በድካማቸው የሚወቀሱትና ደግሞም መፍትሄ ፍለጋ በተለያዩና መጽሓፍ ቅዱሳዊ ባልሆኑ መንገዶች የሚንከራተቱት ስለኃጢአታቸውና ስለድካማቸው የተከፈለውን ይህንን የከበረ ዋጋ በትክክል የሚያሳያቸው እረኛ በማጣታቸው ነው:: ዛሬም ለእነዚህ ወንድሞቻችንና እሕቶቻችን የእግዚአብሔር መንፈስ ያለው ሓዋርያዊ መልእክት "ልጆች ሆይ ኃጢአትን እንዳታድርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ:: ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: እርሱም የኃጢአታችን ማስተሰረያ ነው::" የሚለው ነው:: (የሚቀጥል)
No comments:
Post a Comment