by Tibebe Belay on Monday, January 30, 2012 at 7:29am
ልጅነት!(ካለፈው የቀጠለ)
"ልጆች ሆይ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ: ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው:: ለኃጢአታችን ብቻ አይደለም: ነገር ግን ለዓለም ሁሉ ኃጢአት እንጂ::" 1ዮሃ.2:1-2
ከአለም ፍጥረት ጀምሮ ከታረደው በግ የተነሳ በዘመናት መካከል የተገለጠውና የሚገለጠው የእግዚአብሔር ምሕረት ፍጻሜና ወሰን የለውም:: በዚህ ዘመን ያሉ መንፈሳዊ ሕጻናት ሊረዱት የሚገባው ነገር ይህ ነው:: በልጅነታችን ዘመን የምንፈጽማቸው ኃጢአቶች በእግዚአብሔር ዘንድ ያለውን የምሕረት ጉልበት አይገዳደሩትም:: እርሱም የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ያስወገደው የእግዚአብሔር በግ ነው:: የሰማዩ አባት ከስጋችን ድካምና በልጁ ሕይወት ካለማደጋችን የተነሳ ትናንት የፈጸምነውን በደል አያስታውሰውም:: ዛሬና ነገ ልንፈጽማቸው የምንችላቸውን ስሕተቶችም በቀራንዮ መስቀል ላይ ከተሰዋው በግ የተነሳ በፊቱ የሉም:: ከሳሻችን ዲያብሎስ የሚመዘው የክስ መዝገብ ሁሉ በሰማያዊው ችሎት ከአብ ዘንድ ካለን ጻድቅ ጠበቃ የተነሳ ውድቅ ናቸው::
በዚህ ዘመን ያሉ መንፈሳዊ ሕጻናት በክርስቶስ የተገለጠውን የእግዚአብሔር ፍቅር, ጸጋና ምሕረት በሙላት እንዳያጣጥሙ የሚከላከላቸው; ከውጭም (ሰዎችንና ሁኔታዎችን እየተጠቀመ) ከውስጥም (ባልበሰለውና ባላደገው አእምሮና ህሊናቸው አማካኝነት) ሆኖ የሚከሳቸው ከሳሽ ዲያብሎስ ነው:: ልጆች ሆይ! ዛሬ አንድ የምስራች እነግራችኋለሁ:: በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት የሚባል ነገር የለም:: እርሱ አምላካችን ይህንን ችግር ለአንዼና ለመጨረሻ ጊዜ በቀራንዮ መስቀል ላይ ፈጽሞ አስወግዶታል:: ይሄ ተራ የሃይማኖት ዶክትሪን አይደለም:: በመስቀሉ ላይ የተፈጸመውን ይህን የከበረ የእግዚአብሔር ሥራ ማየት ይሆንላችሁ ዘንድ እግዚአብሔር የልቦናችሁን ዓይኖች ያብራ!!
በኃጢአታችን ምክንያት ጠላት በአእምሮችን ላይ የሚያመጣው ክስና ተጽእኖ በራሱ እስራት ነው:: ዛሬ ብዙዎቻችን ክርስቲያኖች ሆነን, ደግሞም የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን መንፈሳችን እየመሰከረልን ነገር ግን ገና ከሞት ፍርሃት ፈጽመን ነጻ መውጣት ያልቻልንበት ምክንያት ጠላት በአእምሮአችንና በህሊናችን ውስጥ ከሚፈጥረው የኃጢአት ክስ የተነሳ ነው:: ነገር ግን ከቡር በሆነው የክርስቶስ ደም አንድ ጊዜ በተከፈለው ዋጋ የመዋጀታችን ምሥጢር ከእግዚአብሔር ዘንድ በሚመጣ ሰማያዊ መገለጥና ብርሃን ሲበራልን, በህይወታችን ዙሪያ በምናያቸው መንፈሳዊ ድካሞች አንከሰስም::
ኃጢአት ምንጩ ስጋዊ አእምሮ ነው:: ከዚህ አእምሮ ፈጽሞ ነጻ መውጣት እስኪሆንልን ድረስ በኃጢአት ድካም መኖራችን ግድ ነው:: በመጀመሪያዎቹ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ዘንድ ይታይ የነበረው ድካም (ቅናት, ክርክር, መለያየት...) በክርስቶስ አእምሮ ያለማደጋቸውና ከስጋዊ አእምሮ ያለመላቀቃቸው ውጤት ነው:: ሓዋርያው ጳውሎስ በዚህ ድካማቸው አልፈረደባቸውም:: ይልቁኑም ከዚህ ድካም ይበረቱ ዘንድ የሚያስችላቸውንና ላሉበት መንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ የሚመጥናቸውን የወተት ቃል (መሰረታዊ የክርስትና ትምህርቶች) እንደመገባቸው የተናገረውን ቃል በ1ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 3:1-4 እንዲህ ተጽፎ እናገኘዋለን:: "እኔም ወንድሞች ሆይ የስጋ እንደመሆናችሁ በክርስቶስም ሕጻናት እንደሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልኩም:: ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበረና ወተት ጋትኋችሁ: ገና ስጋውያን ናችሁና እስከ አሁን ድረስ አትችሉም:: ቅናትና ክርክር ስለሚገኝባችሁ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደላችሁምን? እንደ:- ሰው ልማድስ አትመላለሱምን? አንዱ እኔ የጳውሎስ ነኝ, ሁለተኛውም:- እኔ የአጵሎስ ነኝ ቢል ሰዎች ብቻ መሆናችሁ አይደለምን?" (ዛሬ በዚህ ዘመን የሚገኙ ወንድሞቼም አንዱ:- እኔ "ኦርቶዶክሳዊ" ነኝ ቢል, ሁለተኛውም :- እኔስ "ፕሮቴስታንት" ነኝ ቢል, በመካከላቸውም ቅናትና ክርክር, መለያየትና ስድብ... ቢኖር ሰዎች ብቻ መሆናቸው አይደለምን? ደግሞም ሕጻናትና ሥጋውያን ናቸውና የሚያስፈልጋቸው ጠንካራ ምግብ ሳይሆን ወተት ነው::)
ከላይ እንዳልነው ክቡር በሆነው በክርስቶስ ደም የመዋጀታችን ምሥጢር ሲገባን ዛሬ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ላይ በምናየው ድካም አንከሰስም:: ይሄ ማለት ግን እለት እለት ኃጢአትን እንደውሃ የመጨለጥ ነጻነት እናገኛለን ማለት አይደለም:: ደሙ የሰጠን ነጻነት ሕያው እግዚአብሔርን በእውነትና በመንፈስ ሆነን የምናመልክበትን ነጻነት ነው:: እግዚአብሔርን በክርስቶስ ኢየሱስ ሆነን በነጻነት ስናመልክ ደግሞ ከክብሩ ዙፋን የሚፈሰው ጸጋና ምህረት ከአፉም የሚወጣው ህያው ቃል የዕለት እንጀራችን ይሆናል:: ያኔ ዕለት - ዕለት አእምሮአችን እየታደሰ, በአንድ በኩል ጠላት በኃጢአታችን ምክንያት ከሚያመጣብን ክስ ነጻ እየወጣን በሌላ በኩል ደግሞ የኃጢአት ምንጭ ከሆነው ስጋዊ አእምሮ እየተላቀቅን እንመጣለን::(የሚቀጥል)
"ልጆች ሆይ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ: ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው:: እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው:: ለኃጢአታችን ብቻ አይደለም: ነገር ግን ለዓለም ሁሉ ኃጢአት እንጂ::" 1ዮሃ.2:1-2
ከአለም ፍጥረት ጀምሮ ከታረደው በግ የተነሳ በዘመናት መካከል የተገለጠውና የሚገለጠው የእግዚአብሔር ምሕረት ፍጻሜና ወሰን የለውም:: በዚህ ዘመን ያሉ መንፈሳዊ ሕጻናት ሊረዱት የሚገባው ነገር ይህ ነው:: በልጅነታችን ዘመን የምንፈጽማቸው ኃጢአቶች በእግዚአብሔር ዘንድ ያለውን የምሕረት ጉልበት አይገዳደሩትም:: እርሱም የዓለምን ሁሉ ኃጢአት ያስወገደው የእግዚአብሔር በግ ነው:: የሰማዩ አባት ከስጋችን ድካምና በልጁ ሕይወት ካለማደጋችን የተነሳ ትናንት የፈጸምነውን በደል አያስታውሰውም:: ዛሬና ነገ ልንፈጽማቸው የምንችላቸውን ስሕተቶችም በቀራንዮ መስቀል ላይ ከተሰዋው በግ የተነሳ በፊቱ የሉም:: ከሳሻችን ዲያብሎስ የሚመዘው የክስ መዝገብ ሁሉ በሰማያዊው ችሎት ከአብ ዘንድ ካለን ጻድቅ ጠበቃ የተነሳ ውድቅ ናቸው::
በዚህ ዘመን ያሉ መንፈሳዊ ሕጻናት በክርስቶስ የተገለጠውን የእግዚአብሔር ፍቅር, ጸጋና ምሕረት በሙላት እንዳያጣጥሙ የሚከላከላቸው; ከውጭም (ሰዎችንና ሁኔታዎችን እየተጠቀመ) ከውስጥም (ባልበሰለውና ባላደገው አእምሮና ህሊናቸው አማካኝነት) ሆኖ የሚከሳቸው ከሳሽ ዲያብሎስ ነው:: ልጆች ሆይ! ዛሬ አንድ የምስራች እነግራችኋለሁ:: በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት የሚባል ነገር የለም:: እርሱ አምላካችን ይህንን ችግር ለአንዼና ለመጨረሻ ጊዜ በቀራንዮ መስቀል ላይ ፈጽሞ አስወግዶታል:: ይሄ ተራ የሃይማኖት ዶክትሪን አይደለም:: በመስቀሉ ላይ የተፈጸመውን ይህን የከበረ የእግዚአብሔር ሥራ ማየት ይሆንላችሁ ዘንድ እግዚአብሔር የልቦናችሁን ዓይኖች ያብራ!!
በኃጢአታችን ምክንያት ጠላት በአእምሮችን ላይ የሚያመጣው ክስና ተጽእኖ በራሱ እስራት ነው:: ዛሬ ብዙዎቻችን ክርስቲያኖች ሆነን, ደግሞም የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን መንፈሳችን እየመሰከረልን ነገር ግን ገና ከሞት ፍርሃት ፈጽመን ነጻ መውጣት ያልቻልንበት ምክንያት ጠላት በአእምሮአችንና በህሊናችን ውስጥ ከሚፈጥረው የኃጢአት ክስ የተነሳ ነው:: ነገር ግን ከቡር በሆነው የክርስቶስ ደም አንድ ጊዜ በተከፈለው ዋጋ የመዋጀታችን ምሥጢር ከእግዚአብሔር ዘንድ በሚመጣ ሰማያዊ መገለጥና ብርሃን ሲበራልን, በህይወታችን ዙሪያ በምናያቸው መንፈሳዊ ድካሞች አንከሰስም::
ኃጢአት ምንጩ ስጋዊ አእምሮ ነው:: ከዚህ አእምሮ ፈጽሞ ነጻ መውጣት እስኪሆንልን ድረስ በኃጢአት ድካም መኖራችን ግድ ነው:: በመጀመሪያዎቹ የቆሮንቶስ ክርስቲያኖች ዘንድ ይታይ የነበረው ድካም (ቅናት, ክርክር, መለያየት...) በክርስቶስ አእምሮ ያለማደጋቸውና ከስጋዊ አእምሮ ያለመላቀቃቸው ውጤት ነው:: ሓዋርያው ጳውሎስ በዚህ ድካማቸው አልፈረደባቸውም:: ይልቁኑም ከዚህ ድካም ይበረቱ ዘንድ የሚያስችላቸውንና ላሉበት መንፈሳዊ ሕይወት ደረጃ የሚመጥናቸውን የወተት ቃል (መሰረታዊ የክርስትና ትምህርቶች) እንደመገባቸው የተናገረውን ቃል በ1ኛ ቆሮንቶስ ምዕራፍ 3:1-4 እንዲህ ተጽፎ እናገኘዋለን:: "እኔም ወንድሞች ሆይ የስጋ እንደመሆናችሁ በክርስቶስም ሕጻናት እንደሆናችሁ እንጂ መንፈሳውያን እንደሆናችሁ ልናገራችሁ አልቻልኩም:: ገና ጽኑ መብል ለመብላት አትችሉም ነበረና ወተት ጋትኋችሁ: ገና ስጋውያን ናችሁና እስከ አሁን ድረስ አትችሉም:: ቅናትና ክርክር ስለሚገኝባችሁ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደላችሁምን? እንደ:- ሰው ልማድስ አትመላለሱምን? አንዱ እኔ የጳውሎስ ነኝ, ሁለተኛውም:- እኔ የአጵሎስ ነኝ ቢል ሰዎች ብቻ መሆናችሁ አይደለምን?" (ዛሬ በዚህ ዘመን የሚገኙ ወንድሞቼም አንዱ:- እኔ "ኦርቶዶክሳዊ" ነኝ ቢል, ሁለተኛውም :- እኔስ "ፕሮቴስታንት" ነኝ ቢል, በመካከላቸውም ቅናትና ክርክር, መለያየትና ስድብ... ቢኖር ሰዎች ብቻ መሆናቸው አይደለምን? ደግሞም ሕጻናትና ሥጋውያን ናቸውና የሚያስፈልጋቸው ጠንካራ ምግብ ሳይሆን ወተት ነው::)
ከላይ እንዳልነው ክቡር በሆነው በክርስቶስ ደም የመዋጀታችን ምሥጢር ሲገባን ዛሬ በመንፈሳዊ ሕይወታችን ላይ በምናየው ድካም አንከሰስም:: ይሄ ማለት ግን እለት እለት ኃጢአትን እንደውሃ የመጨለጥ ነጻነት እናገኛለን ማለት አይደለም:: ደሙ የሰጠን ነጻነት ሕያው እግዚአብሔርን በእውነትና በመንፈስ ሆነን የምናመልክበትን ነጻነት ነው:: እግዚአብሔርን በክርስቶስ ኢየሱስ ሆነን በነጻነት ስናመልክ ደግሞ ከክብሩ ዙፋን የሚፈሰው ጸጋና ምህረት ከአፉም የሚወጣው ህያው ቃል የዕለት እንጀራችን ይሆናል:: ያኔ ዕለት - ዕለት አእምሮአችን እየታደሰ, በአንድ በኩል ጠላት በኃጢአታችን ምክንያት ከሚያመጣብን ክስ ነጻ እየወጣን በሌላ በኩል ደግሞ የኃጢአት ምንጭ ከሆነው ስጋዊ አእምሮ እየተላቀቅን እንመጣለን::(የሚቀጥል)
No comments:
Post a Comment