መቼስ
እኛ ኢትዮጵያውያን ራሳችንን ከዓለም የለየንባቸው ምክንያቶች አጅግ ብዙ ናቸው። ሌላው ሕዝብ የራሱ የሆነ ወግና ባህል የሌለው ይመስል
በወጎቻችንና በባህሎቻችን ያለመጠን እንመካለን። በሌላው ዓለም ተራራና ሸለቆ፣ ወንዝና ተረተር፣ ሜዳና ኮረብታ…. የሌለ ይመስል
በመልክዓ ምድራችን ሳይቀር እንኮፈሳለን። …. ዓለምንና ሞላዋን የፈጠረው እግዚአብሔርስ ቢሆን፣ ከሌሎቹ አገሮች ይልቅ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን
የተለየ አጀንዳ፣ የተለየ እንክብካቤ፣…. የተለየ ጉዳይ እንዳለው እናስባለን። የብሉይ ኪዳኑ የእግዚአብሔር ሕዝብ እስራኤላውያን
እንደነበሩ ሁሉ፤ እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ያደረገው አዲስ ኪዳን በዓለም ከሚኖሩ ሕዝቦች ይልቅ ከእኛ ከኢትዮጵውያኑ
ጋር እስኪመስል ድረስ “የክርስቲያን ደሴት” የሚል “የክርስትና ስም” ለራሳችን አውጥተናል።
ሰሞኑን በአንድ የውጭ አገር ኤምባሲ ቢሮ ውስጥ ድንገት የተገናኝን ስድስት የምንሆን ኢትዮጵያውያን ያደረግነው ውይይት ነው ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ። ከስድስታችን ውስጥ ሁለቱ ከሃያ ዓመታት በፊት ዩኒቨርስቲ ውስጥ አብረው ይማሩ የነበሩና ይኖሩበት ከነበረው “የባዕድ ምድር” ከረዥም ጊዜ በሗላ ተመልሰው በድንገት እዚያው ቢሮ ውስጥ የተገናኙ ጓደኛሞች ናቸው። የሌሎቹን ጓደኞቻቸውን ስም እየጠሩ ያሉበትን ይጠያየቃሉ፤ በጣም በሚገርም ሁኔታ ሁሉም ከኢትዮጵያ ውጪ ናቸው። “ከሁሉ በላይ እኔን የሚያበሳጨኝ” አለ አንደኛው፤ “ከሁሉ በላይ እኔን የሚያበሳጨኝ ፊደል ቆጥሬ ዲግሪዬን እስከምይዝ ድረስ በነጻ ያሰተማረችኝን አገሬን መጥቀም ያለመቻሌ ነው።”
ከዚህ ወንድም የቁጭት ንግግር ቀጥሎ፣ ኢትዮጵያ ለአያሌ ዘመናት በድህነትና በችግር እየማቀቀች ባለችበት ሁኔታ ውስጥ፣ አገራቸውን በእጅጉ ሊጠቅሙና የሕዝባቸውን ኑሮ ሊለውጡ የሚችሉ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ለየባዕድ አገሩ በዶላር የሚሸጡበትን ምክንያት እየተነተነና የአገሪቱን የፖለቲካ ሥርዓት እየኮነነ ውይይቱ ቀጠለ። በዚህ መኸል አንዲት እህት፡- “እኔ ግን ኢትዮጵያ ላይ እየደረሰ ላለው መከራና ችግር ምክንያቱ የፖለቲካ ሥርዓቱ ብቻ አይመስለኝም” አለች። ሌላ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማወቅ የጓጉ ወደ አሥር የሚጠጉ አይኖች ልጅቷ ላይ አፈጠጡ። “ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴትና ቅድስት አገር ከመሆኗ የተነሳ ዲያብሎስ ያመጣብን ፈተና ነው” አለች። የሁሉም ሰው ስሜት ሟሸሸ። አሁን እኔን የሚመለከተኝ ርዕስ በመከፈቱ ጉሮሮዬን ጠራረኩና- “አይደለም የኔ እሕት፤ ነገሩ የተገላቢጦሽ ነው” ከማለቴ እነዚያ አይኖች በሙሉ እኔ ላይ አፈጠጡ። “በምድራችን ላይ ዘመናትን ላስቆጠረው ችግርና ጉስቁልና ምክንያቶቹ፣ ጠንክረን ካለመስራታችን ጋር ተዳምሮ፣ በክርስትና ስም የሚደረገው ባዕድ አምልኮ ያመጣብን መርገም ነው” አልኩ ፍርጥም ብዬ።
ለመላእክትና ለሰዎች በተሰጡት ሰላሣ ቀናት ውስጥ የሚከበሩት በዓላት፣ ወደመላእክትና ወደሰዎች የሚደረጉት የልመናና የምልጃ ጸሎቶች፣ ስለ መላእክትና ስለሰዎች የተጻፉትና ‘በየእለተ ቀናቸው’ የሚነበቡት ድርሳናት፣ ለመላእክትና ለሰዎች ምስል የሚደረጉት ስግደቶች፣ ለመላእክትና ለሰዎች የሚቀርቡት የምስጋና እና የውዳሴ መዝሙሮች፣ በመላእክትና በሰዎች ስም የተሰሩት ሕንጻዎችና ሕንጻዎቹም የሚታጠኑት የዕጣንና የሰንደል መዓዛ፣ በመላእክትና በሰዎች ስም ለተሰየሙ “ታቦታት” የሚቀርበው እልልታና ዝማሬ፣ ሽብሸባና ውዳሴ፣ መስዋእትና ስለት፣ አምልኮና ስግደት….. የአገራችንን ክርስትና ለየት ያለና “ቀለመ - ደማቅ” አድርገውት “ነጫጭ ቱሪስቶችን” ወደ አገሪቱ ከመጥራታቸው ቀጥሎ፤ የኢትዮጵያውያኑ እጆች ወደ እግዚአብሔር ሳይሆን ወደ “ነጫጮቹ ለጋሽ አገሮች” እንዲዘረጋ ያደረጉና፣ አገራቸውን በእጅጉ ሊጠቅሙና የሕዝባቸውን ኑሮ ሊለውጡ የሚችሉ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በዓለም ዙሪያ ሁሉ የበተኑ የምድሪቱ መርገሞች ናቸው።
ደግሜ ልናገር!! ‘ኢትዮጵያ’ ተብላ የምትጠራው ምድር ከላይ በተዘረዘሩትና በክርስትና ስም ከሚደረጉት ባዕድ አምልኮዎች የተነሳ፣ የእግዚአብሔር እጅ የከበደባትና ከእርግማን በታች የወደቀች ምድር ነች። ከዚህ እርግማን ነጻ የሚያወጣት ደግሞ በአጭሩ የክርስቶስ ወንጌል ነው። ክርስትና የምንለው ክርስቶስ የመሠረተውንና ሐዋርያት የሰበኩትን እምነት ከሆነ፤ “የእምነታችን ጀማሪና ፈጻሚ” የሆነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ባስተማራቸው ትምሕርቶችም ሆነ እግር - ከእግር የተከተሉት ሐዋርያቱ በሰበኳቸው ወንጌላትና በጻፏቸው መልእክቶች ውስጥ፤ ከላይ እንዳየናቸው ያሉ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የምናገኛቸው ክርስቲያናዊ “ልማዶች” የሉም። እንግዲያውስ ከእውነተኛው ክርስትና አንጻር “መጤ” የሆነውም ሆነ በምንፍቅና ሊፈረጅ የሚገባው፣ ደግሞም የምድሪቱና የሕዝቧ መርገም ምክንያት፣ ይኸው በኢትዮጵያ ውስጥ ለዘመናት እግሩን አንፈራጦ የሚገኘው በክርስትና ስም የሚደረገው “ባዕድ አምልኮ” ነው።
በሌላው ዓለም እንደሚገኙት ሕዝቦች ሁሉ ወደ እውነት የሚመራቸውን የክርስቶስ ወንጌል ካለመስማታቸው ወይም ሰምተው ካለመቀበላቸውና ካለማመናቸው የተነሳ፤ በፈጣሪ ፈንታ የተፈጠሩትን የሚያመልኩ ሰዎች በኢትዮጵያም ውስጥ በብዛት ይገኛሉ። እነዚህም ሰዎች አወቁትም - አላወቁትም ለራሳቸውና ለምድራቸው የመርገም ምክንያቶች ናቸው። ነገር ግን በአንድ እጃቸው ነጻ የሚያወጣውን ወንጌል፣ በሌላ እጃቸው ደግሞ “ልዩ ወንጌል”ይዘው፤ በአንዱ ምላሳቸው ክርስቶስን፣ በሁለተኛው ደግሞ መላእክትንና ሰዎችን የሚሰብኩት፣ ባለማወቃቸው ወይም ባለማመናቸው ምክንያት ዛፍና እንሰሳ የመሳሰሉትን ከሚያመልኩት ሰዎች ይልቅ በራሳቸውም ሆነ በምድራቸው ላይ የከፋ ፍርድንና መርገምን በሚያመጣ ባእድ አምልኮ ውስጥ ናቸው።
በቀደመው ኪዳን በእግዚአብሔር በራሱ ተሰጥቶ የነበረውን የግርዘት ሕግ ወደ አዲሱ ኪዳን የጸጋ ሥርዓት ሊቀላቅሉ የነበሩትን እነ ኬፋን ፊት ለፊት የተቃወመው ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ለገላትያ ክርስቲያኖች በጻፈው መልክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውስጥ፡- “ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፣ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን!” እያለ መላእክት እንኳን ሳይቀሩ ሌላ ወንጌል ቢሰብኩ ከመርገም እንደማያመልጡ ካስጠነቀቀ፤ እንኪያስ! በሕጉና በነቢያት ያልተጻፈውን፣ በክርስቶስ ወንጌል ያልተሰበከውን እንዲህ ያለ እንግዳ ትምሕርት ወደ ክርስትና ጨምረው፣ ዛሬም ድረስ ያለ እፍረት እየሰበኩና እያስተማሩ፣ እያሳቱና እየሳቱ የክርስቶስን ወንጌል የሚያጣምሙት የሐይማኖት ልጆች፣ ምድራቸውም ሆነች ራሳቸው ከዚህ ሐዋርያዊ እርግማን እንዴት ሊያመልጡ ይችላሉ?? በጭራሽ አይችሉም!!!!!
ስለዚህ ወንጌል የረገማትን ይህችን ምድር ከዚህ እርግማን ነጻ ሊያወጣት የሚችለው ያው የረገማት ወንጌል ብቻ ነው። የወንጌሉ ባለቤት የሆነውና ከሰማይ በታች ያሉ ሰዎች ሁሉ (ኢትይጵያውያንም ሳይቀሩ) በእምነት እየጠሩ ይድኑበት ዘንድ የተሰጣቸው አንድ ስም ነው። ክርስቶስና ጌታ የሆነው የሕያው እግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ስም!!! ይህ በምድርም ሆነ በሰማያት ከሚጠሩት ስሞች ሁሉ በላይ ከፍ ከፍ ያለው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በምድሪቱ ሰማያት ላይ ብቻውን መንገስ፣ ብቻውን መወደስ፣ ብቻውን መጠራት፣…. ሲጀምር፤ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እውነተኛው የእግዚአብሔር ክብር ይመጣል። ብዙዎች ከጨለማው ገዢ እሥራት ማምለጥ ይሆንላቸዋል፣ የምድሪቱ መርገም መሰባበር ይጀምራል፣ በሥፍራ ሁሉ የተበታተኑ፣ ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ለባዕዳን አገሮች እየሸጡ ያሉና ሕዛባቸውንና ምድራቸውን በእጅጉ ሊጠቅሙ የሚችሉ አያሌ ኢትዮጵያውያን ወደ ምድራቸው መመለስ ይጀምራሉ። ከዚህም በላይ፤ ኢትዮጵያውያንም የወንጌል ትሩፋት የሆነውንና በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነው እምነት በኩል ብቻ ሊገኝ የሚችለው ሰማያዊ በረከት ተካፋይ ይሆናሉ። እግዚአብሔር ሆይ!! በዚህ በእኛ ዘመን በምድራችን ላይ ይህን ለማድረግ ቆርጠህ ስለተነሳህ ተመስገን!!! በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ለዘላለሙ አሜን!!!!!
ሰሞኑን በአንድ የውጭ አገር ኤምባሲ ቢሮ ውስጥ ድንገት የተገናኝን ስድስት የምንሆን ኢትዮጵያውያን ያደረግነው ውይይት ነው ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ። ከስድስታችን ውስጥ ሁለቱ ከሃያ ዓመታት በፊት ዩኒቨርስቲ ውስጥ አብረው ይማሩ የነበሩና ይኖሩበት ከነበረው “የባዕድ ምድር” ከረዥም ጊዜ በሗላ ተመልሰው በድንገት እዚያው ቢሮ ውስጥ የተገናኙ ጓደኛሞች ናቸው። የሌሎቹን ጓደኞቻቸውን ስም እየጠሩ ያሉበትን ይጠያየቃሉ፤ በጣም በሚገርም ሁኔታ ሁሉም ከኢትዮጵያ ውጪ ናቸው። “ከሁሉ በላይ እኔን የሚያበሳጨኝ” አለ አንደኛው፤ “ከሁሉ በላይ እኔን የሚያበሳጨኝ ፊደል ቆጥሬ ዲግሪዬን እስከምይዝ ድረስ በነጻ ያሰተማረችኝን አገሬን መጥቀም ያለመቻሌ ነው።”
ከዚህ ወንድም የቁጭት ንግግር ቀጥሎ፣ ኢትዮጵያ ለአያሌ ዘመናት በድህነትና በችግር እየማቀቀች ባለችበት ሁኔታ ውስጥ፣ አገራቸውን በእጅጉ ሊጠቅሙና የሕዝባቸውን ኑሮ ሊለውጡ የሚችሉ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ለየባዕድ አገሩ በዶላር የሚሸጡበትን ምክንያት እየተነተነና የአገሪቱን የፖለቲካ ሥርዓት እየኮነነ ውይይቱ ቀጠለ። በዚህ መኸል አንዲት እህት፡- “እኔ ግን ኢትዮጵያ ላይ እየደረሰ ላለው መከራና ችግር ምክንያቱ የፖለቲካ ሥርዓቱ ብቻ አይመስለኝም” አለች። ሌላ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማወቅ የጓጉ ወደ አሥር የሚጠጉ አይኖች ልጅቷ ላይ አፈጠጡ። “ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴትና ቅድስት አገር ከመሆኗ የተነሳ ዲያብሎስ ያመጣብን ፈተና ነው” አለች። የሁሉም ሰው ስሜት ሟሸሸ። አሁን እኔን የሚመለከተኝ ርዕስ በመከፈቱ ጉሮሮዬን ጠራረኩና- “አይደለም የኔ እሕት፤ ነገሩ የተገላቢጦሽ ነው” ከማለቴ እነዚያ አይኖች በሙሉ እኔ ላይ አፈጠጡ። “በምድራችን ላይ ዘመናትን ላስቆጠረው ችግርና ጉስቁልና ምክንያቶቹ፣ ጠንክረን ካለመስራታችን ጋር ተዳምሮ፣ በክርስትና ስም የሚደረገው ባዕድ አምልኮ ያመጣብን መርገም ነው” አልኩ ፍርጥም ብዬ።
ለመላእክትና ለሰዎች በተሰጡት ሰላሣ ቀናት ውስጥ የሚከበሩት በዓላት፣ ወደመላእክትና ወደሰዎች የሚደረጉት የልመናና የምልጃ ጸሎቶች፣ ስለ መላእክትና ስለሰዎች የተጻፉትና ‘በየእለተ ቀናቸው’ የሚነበቡት ድርሳናት፣ ለመላእክትና ለሰዎች ምስል የሚደረጉት ስግደቶች፣ ለመላእክትና ለሰዎች የሚቀርቡት የምስጋና እና የውዳሴ መዝሙሮች፣ በመላእክትና በሰዎች ስም የተሰሩት ሕንጻዎችና ሕንጻዎቹም የሚታጠኑት የዕጣንና የሰንደል መዓዛ፣ በመላእክትና በሰዎች ስም ለተሰየሙ “ታቦታት” የሚቀርበው እልልታና ዝማሬ፣ ሽብሸባና ውዳሴ፣ መስዋእትና ስለት፣ አምልኮና ስግደት….. የአገራችንን ክርስትና ለየት ያለና “ቀለመ - ደማቅ” አድርገውት “ነጫጭ ቱሪስቶችን” ወደ አገሪቱ ከመጥራታቸው ቀጥሎ፤ የኢትዮጵያውያኑ እጆች ወደ እግዚአብሔር ሳይሆን ወደ “ነጫጮቹ ለጋሽ አገሮች” እንዲዘረጋ ያደረጉና፣ አገራቸውን በእጅጉ ሊጠቅሙና የሕዝባቸውን ኑሮ ሊለውጡ የሚችሉ አያሌ ኢትዮጵያውያንን በዓለም ዙሪያ ሁሉ የበተኑ የምድሪቱ መርገሞች ናቸው።
ደግሜ ልናገር!! ‘ኢትዮጵያ’ ተብላ የምትጠራው ምድር ከላይ በተዘረዘሩትና በክርስትና ስም ከሚደረጉት ባዕድ አምልኮዎች የተነሳ፣ የእግዚአብሔር እጅ የከበደባትና ከእርግማን በታች የወደቀች ምድር ነች። ከዚህ እርግማን ነጻ የሚያወጣት ደግሞ በአጭሩ የክርስቶስ ወንጌል ነው። ክርስትና የምንለው ክርስቶስ የመሠረተውንና ሐዋርያት የሰበኩትን እምነት ከሆነ፤ “የእምነታችን ጀማሪና ፈጻሚ” የሆነው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ባስተማራቸው ትምሕርቶችም ሆነ እግር - ከእግር የተከተሉት ሐዋርያቱ በሰበኳቸው ወንጌላትና በጻፏቸው መልእክቶች ውስጥ፤ ከላይ እንዳየናቸው ያሉ በተለይ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የምናገኛቸው ክርስቲያናዊ “ልማዶች” የሉም። እንግዲያውስ ከእውነተኛው ክርስትና አንጻር “መጤ” የሆነውም ሆነ በምንፍቅና ሊፈረጅ የሚገባው፣ ደግሞም የምድሪቱና የሕዝቧ መርገም ምክንያት፣ ይኸው በኢትዮጵያ ውስጥ ለዘመናት እግሩን አንፈራጦ የሚገኘው በክርስትና ስም የሚደረገው “ባዕድ አምልኮ” ነው።
በሌላው ዓለም እንደሚገኙት ሕዝቦች ሁሉ ወደ እውነት የሚመራቸውን የክርስቶስ ወንጌል ካለመስማታቸው ወይም ሰምተው ካለመቀበላቸውና ካለማመናቸው የተነሳ፤ በፈጣሪ ፈንታ የተፈጠሩትን የሚያመልኩ ሰዎች በኢትዮጵያም ውስጥ በብዛት ይገኛሉ። እነዚህም ሰዎች አወቁትም - አላወቁትም ለራሳቸውና ለምድራቸው የመርገም ምክንያቶች ናቸው። ነገር ግን በአንድ እጃቸው ነጻ የሚያወጣውን ወንጌል፣ በሌላ እጃቸው ደግሞ “ልዩ ወንጌል”ይዘው፤ በአንዱ ምላሳቸው ክርስቶስን፣ በሁለተኛው ደግሞ መላእክትንና ሰዎችን የሚሰብኩት፣ ባለማወቃቸው ወይም ባለማመናቸው ምክንያት ዛፍና እንሰሳ የመሳሰሉትን ከሚያመልኩት ሰዎች ይልቅ በራሳቸውም ሆነ በምድራቸው ላይ የከፋ ፍርድንና መርገምን በሚያመጣ ባእድ አምልኮ ውስጥ ናቸው።
በቀደመው ኪዳን በእግዚአብሔር በራሱ ተሰጥቶ የነበረውን የግርዘት ሕግ ወደ አዲሱ ኪዳን የጸጋ ሥርዓት ሊቀላቅሉ የነበሩትን እነ ኬፋን ፊት ለፊት የተቃወመው ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ለገላትያ ክርስቲያኖች በጻፈው መልክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ውስጥ፡- “ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፣ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን!” እያለ መላእክት እንኳን ሳይቀሩ ሌላ ወንጌል ቢሰብኩ ከመርገም እንደማያመልጡ ካስጠነቀቀ፤ እንኪያስ! በሕጉና በነቢያት ያልተጻፈውን፣ በክርስቶስ ወንጌል ያልተሰበከውን እንዲህ ያለ እንግዳ ትምሕርት ወደ ክርስትና ጨምረው፣ ዛሬም ድረስ ያለ እፍረት እየሰበኩና እያስተማሩ፣ እያሳቱና እየሳቱ የክርስቶስን ወንጌል የሚያጣምሙት የሐይማኖት ልጆች፣ ምድራቸውም ሆነች ራሳቸው ከዚህ ሐዋርያዊ እርግማን እንዴት ሊያመልጡ ይችላሉ?? በጭራሽ አይችሉም!!!!!
ስለዚህ ወንጌል የረገማትን ይህችን ምድር ከዚህ እርግማን ነጻ ሊያወጣት የሚችለው ያው የረገማት ወንጌል ብቻ ነው። የወንጌሉ ባለቤት የሆነውና ከሰማይ በታች ያሉ ሰዎች ሁሉ (ኢትይጵያውያንም ሳይቀሩ) በእምነት እየጠሩ ይድኑበት ዘንድ የተሰጣቸው አንድ ስም ነው። ክርስቶስና ጌታ የሆነው የሕያው እግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ስም!!! ይህ በምድርም ሆነ በሰማያት ከሚጠሩት ስሞች ሁሉ በላይ ከፍ ከፍ ያለው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በምድሪቱ ሰማያት ላይ ብቻውን መንገስ፣ ብቻውን መወደስ፣ ብቻውን መጠራት፣…. ሲጀምር፤ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እውነተኛው የእግዚአብሔር ክብር ይመጣል። ብዙዎች ከጨለማው ገዢ እሥራት ማምለጥ ይሆንላቸዋል፣ የምድሪቱ መርገም መሰባበር ይጀምራል፣ በሥፍራ ሁሉ የተበታተኑ፣ ጉልበታቸውንና እውቀታቸውን ለባዕዳን አገሮች እየሸጡ ያሉና ሕዛባቸውንና ምድራቸውን በእጅጉ ሊጠቅሙ የሚችሉ አያሌ ኢትዮጵያውያን ወደ ምድራቸው መመለስ ይጀምራሉ። ከዚህም በላይ፤ ኢትዮጵያውያንም የወንጌል ትሩፋት የሆነውንና በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነው እምነት በኩል ብቻ ሊገኝ የሚችለው ሰማያዊ በረከት ተካፋይ ይሆናሉ። እግዚአብሔር ሆይ!! በዚህ በእኛ ዘመን በምድራችን ላይ ይህን ለማድረግ ቆርጠህ ስለተነሳህ ተመስገን!!! በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ለዘላለሙ አሜን!!!!!