“ጽድቅ” ማለት በእግዚአብሔር ሚዛን የሆነ ትክክለኛ ኑሮ ማለት ነው። “ጻድቅ” የሚባለውም እግዚአብሔር “ትክክል ነው” በሚለው መንገድ ኑሮውንና ሕይወቱን የሚመራ ነው። እግዚአብሔር በቀደመው ዘመን እነ ኢዮብን "ጻድቅ" ያለበትንና ኋላም በክርስቶስ በገለጠው የራሱ ጽድቅ መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ማወቁ በእጅጉ አስፈላጊ ነው። እግዚአብሔር በሙሴ በኩል ከሰጠው ሕግ በፊት ይኖሩ የነበሩት እነኢዮብ፣ ኖህና አብርሃምን የመሳሰሉ አባቶች "ጻድቃን" ተብለው የተጠሩት፣ እነርሱ ይኖሩበት በነበረው ዘመን በኖሩት ኑሮ ልክና መጠን ነው። ያ ማለት ግን ኑሮአቸው በእግዚአብሔር ጽድቅ ልክና መጠን ነበር ማለት አይደለም። ምክንያቱም የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠው በክርስቶስ ስለሆነ ነው።
“አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል። እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው…” ሮሜ.3፡21-22
ሕግ የተሰጣቸውን እስራኤላውያንንም ስንመለከት በእነርሱ እንዲገለጥ የተፈለገው ጽድቅ ሕጉ በሚጠይቀው መጠንና ልክ ብቻ ነበር። ይህም ቢሆን ኋላ በክርስቶስ ከተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ ጋር እጅግ ሰፊ የሆነ ልዩነት አለው። ለምሳሌ፡- ሕጉ "አታመንዝር" ሲል፡- ከአንዲቷ ሚስትህ ውጪ ከሌላ ሴት ጋር አትተኛ ማለቱ ነው። ነገር ግን በዚሁ አታመንዝር በሚለው ትዕዛዝ ላይ በክርስቶስ የተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ "ወደሴት ያየ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርሷ ጋር አመንዝሮአል" ይላል። በሕጉ የተገለጠው ትክክለኛ ኑሮ የሚወዱንን መውደድ፣ የሚጠሉንን መጥላት ነው። ነገር ግን በክርስቶስ የተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ፣ ጠላቶቻችንን እንድንወድ፣ የሚረግሙንን እንድንመርቅ፣ ለሚጠሉንም መልካም እንድናደርግ፣ ስለሚያሳድዱን እንድንጸልይ... ያስችለናል።
“አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል። እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው…” ሮሜ.3፡21-22
ሕግ የተሰጣቸውን እስራኤላውያንንም ስንመለከት በእነርሱ እንዲገለጥ የተፈለገው ጽድቅ ሕጉ በሚጠይቀው መጠንና ልክ ብቻ ነበር። ይህም ቢሆን ኋላ በክርስቶስ ከተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ ጋር እጅግ ሰፊ የሆነ ልዩነት አለው። ለምሳሌ፡- ሕጉ "አታመንዝር" ሲል፡- ከአንዲቷ ሚስትህ ውጪ ከሌላ ሴት ጋር አትተኛ ማለቱ ነው። ነገር ግን በዚሁ አታመንዝር በሚለው ትዕዛዝ ላይ በክርስቶስ የተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ "ወደሴት ያየ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርሷ ጋር አመንዝሮአል" ይላል። በሕጉ የተገለጠው ትክክለኛ ኑሮ የሚወዱንን መውደድ፣ የሚጠሉንን መጥላት ነው። ነገር ግን በክርስቶስ የተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ፣ ጠላቶቻችንን እንድንወድ፣ የሚረግሙንን እንድንመርቅ፣ ለሚጠሉንም መልካም እንድናደርግ፣ ስለሚያሳድዱን እንድንጸልይ... ያስችለናል።
ስለዚህ በኢዲሱ ኪዳን ስለተገለጠውና በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ብቻ ስለሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ወይም ትክክለኛ ኑሮ ስናስብ፣ ሰው በራሱ ዐቅምና ብቃት ፈጽሞ ሊኖረው የማይችል እጅግ የከበረና የላቀ የጽድቅ ሕይወት ነው። ይህ "የእግዚአብሔር ጽድቅ" ማንም "የእኔ" ሊለው አይችልም። የእያንዳንዱ ሰው ሕይወት በዚህ የጽድቅ ሚዛን ሲለካ ጎደሎ ነው። ከሥጋና ከደም ከተወለዱ የሰው ልጆች መካከል ማንም በዚህ ጽድቅ ልክ የኖረ የለም። ለዚህም ነው የእግዚአብሔር ቃል፡- "ጻድቅ የለም - አንድ ስንኳ" በማለት አስረግጦ የሚነግረን። በዚህ በክርስቶስ በተገለጠው የእግዚአብሔር ጽድቅ ሚዛን ላይ ብናስቀምጠው፣ ኢዩብም ጻድቅ አይደለም፣ አብርሃምም ሆነ ኖህ፣ ሙሴም ሆነ ዳዊት.... ተክልዬም ሆኑ አቡዬ ጻድቅ አይደሉም። "ጻድቅ የለም - አንድ ስንኳ!!!!!!!!"
ስለዚህ እግዚአብሔር ይሄንን የራሱን ጽድቅ በሰዎች ሕይወት ውስጥ ለማኖርና ለመግለጥ ነው አንድያ ልጁን በሥጋ ወደዚህ ዓለም የላከው። በክርስቶስ እምነት የምንካፈለው የእግዚአብሔርን የራሱን ጽድቅ ነው። ይህም ጽድቅ በእኛ ሕይወት የሚገለጥበት ሁለት ደረጃዎች አሉት። የመጀመሪያው የእግዚአብሔር ጽድቅ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን በጸጋ ብቻ የሚገኝ ነጻ ስጦታ እንደሆነ አምነን የምንቀበልበትና የራሳችን የምናደርግበት ደረጃ ነው። ይህንን ደረጃ፡- Imputed righteousness ይሉታል። የጽድቅ ሕይወትና ኑሮ ገና በእኛ መገለጥ ሳይጀምር፣ በእግዚአብሔር ዓይንና አቆጣጠር ብቻ "ጻድቃን" ተብለን የምንጠራበትና የምንቆጠርበት ደረጃ ነው። "አብርሃምም እግዚአብሔርን አመነ፣ ጽድቅም ሆኖ ተቆጠረለት" የሚለው ቃል ለዚህ ሕያው እውነት ምስክር ነው። የእግዚአብሔር ጽድቅ በሥራ ሳይሆን፣ በእምነት ብቻ የሚገኝ ነው።
"ሥጋን የለበሰ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት እንዳይመካ ፤ነገር ግን የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው።" 1ቆሮ.1፡29-31
ክርስቶስ እርሱ ጽድቃችን ነው፤ የመጀመሪያው ነገር ይሄንን አምኖ መቀበልና በክርስቶስ ባለ እምነት ብቻ "ጻድቅ" ወይም "ቅዱስ" ተብሎ መጠራት ነው። እዚህ ላይ "ጻድቅ" ወይም "ቅዱስ" ተብሎ መጠራትና መሆን የተለያዩ ደረጃዎች ናቸው። ከመሆናችን በፊት መጠራታችን ወይም መቆጠራችን ከመቅደሙም በላይ ለመሆናችን መሠረት ነው። ይህም ገበሬው የስንዴውን መከር ከማጨዱና ከመሰብሰቡ በፊት አስቀድሞ ቅንጣቱን እንደመዝራቱ የሚቆጠር ነው። የጽድቅ ዘር የሆነው ክርስቶስ አስቀድሞ በእኛ ሕይወት ካልተዘራ የጽድቅ ፍሬ የሚባል ነገር የለም። የተወደደው ወንድማችን ጳውሎስ፡- ለፊሊጲስዩስ ቅዱሳን በጻፈው መልእክቱ ውስጥ ይህ እውነት ተገልጦአል፡-
"ለእግዚአብሔርም ክብርና ምስጋና ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚገኝ የጽድቅ ፍሬ ሞልቶባችሁ፥ ለክርስቶስ ቀን ተዘጋጅታችሁ ቅኖችና አለ ነውር እንድትሆኑ የሚሻለውን ነገር ፈትናችሁ ትወዱ ዘንድ፥ ፍቅራችሁ በእውቀትና በማስተዋል ሁሉ ከፊት ይልቅ እያደገ እንዲበዛ ይህን እጸልያለሁ።" ፊሊ.1፡9-11
ስለዚህ በእምነት ከተቀበልነው የጽድቅ ዘር ከክርስቶስ የተነሳ "ጻድቃንና ቅዱሳን" ተብለን መጠራታችን የመጀመሪያው ደረጃ ሲሆን፣ ይህ በእምነት የተቀበልነው የጽድቅ ዘር፣ የጽድቅ ፍሬ የሚሆንበት፣ ወይም በሕይወት አካሄዳችን የሚገለጥበት ደረጃ ደግሞ ሁለተኛው ነው። ይህንንም Imparted Righteousness ይሉታል። በእኛ ያለውን ክርስቶስና ሕይወቱን የምንካፈልበትና የምንኖርበት ደረጃ ነው። በእምነት "ጻድቃን እና ቅዱሳን" ተብለው የተጠሩት ያመኑ ክርስቲያኖች፣ ጽድቃቸውና ቅድስናቸው የሆነው ክርስቶስ በሕይወት አካሄዳቸው እንዲገለጥ፣ በነፍሳቸው ጥልቀት ውስጥ የተዘራው የጽድቅና የቅድስና ዘር - ክርስቶስ የኑአሮቸው ፍሬ እንዲሆን.... "ቅዱሳን ሁኑ፣ ትቀደሱ ዘንድ ፈልጉ፣ ሰውነታችሁን ቅዱስና ሕያው መስዋዕት አድርጋችሁ አቅርቡ...." እየተባሉ ዕለት - ዕለት ይማራሉ፣ ይመከራሉ፣ ይገሰጻሉ፣ ይበረታታሉ!! ይህም በሚገባ አርሶና ጎልጉሎ መልካሙን ዘር የዘራበትን መሬት እንደሚንከባከበው ገበሬ፣ የቃሉ አገልጋዮች የዕለት ተዕለት ሥራ ነው።
እግዚአብሔር በተለይ በወንድማችን ጳውሎስ በኩል በተሰበከው ወንጌል የገለጠው ምሥጢር አንድ ነው። እርሱም የጽድቅ ዘር የሆነው ክርስቶስ በእኛ ውስጥ መሆኑንና በሕይወት አካሄዳችንም የኑሮአችን ፍሬ ሆኖ የሚገለጠው ክርስቶስ ራሱ መሆኑን ነው። የተወደደው ሐዋርያ ይህንን የጽድቅ ዘር በወንጌሉ የዘራባቸውን ቅዱሳን “እናንተ የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ” እያለ፤ ክርስቶስ በእነሱ እስኪሳል ወይም ሕያው ሆኖ እስኪገለጥና የሕይወት አካሄዳቸው ደግሞም የኑሮቸው ፍሬ እስኪሆን ድረስ ዕለት ዕለትእንደ ትጉ ገበሬ አገልግሎቱን ይፈጽም ነበር። የተጋድሎውንም ዓላማ "በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰው ማቅረብ" ብሎታል። ይህም የመንፈሳዊው ገበሬ የድካሙ የመጨረሻ ውጤት ወይም ፍሬው ነው።
“ስለ እናንተ እንደ ተሰጠኝ እንደ እግዚአብሔር መጋቢነት፥ የእግዚአብሔርን ቃል ፈጽሜ እንድሰብክ እኔ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ሆንሁ። ይህም ቃል ከዘላለምና ከትውልዶች ጀምሮ ተሰውሮ የነበረ ምሥጢር ነው፥ አሁን ግን ለቅዱሳኑ ተገልጦአል። ለእነርሱም እግዚአብሔር በአሕዛብ ዘንድ ያለው የዚህ ምሥጢር ክብር ባለ ጠግነት ምን እንደ ሆነ ሊያስታውቅ ወደደ፥ ምሥጢሩም የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ በእናንተ ዘንድ መሆኑ ነው። እኛም በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰውን ሁሉ እናቀርብ ዘንድ ሰውን ሁሉ እየገሠጽን ሰውንም ሁሉ በጥበብ ሁሉ እያስተማርን የምንሰብከው እርሱ ነው። ለዚህም ነገር ደግሞ፥ በእኔ በኃይል እንደሚሠራ እንደ አሠራሩ እየተጋደልሁ፥ እደክማለሁ።” (ቆላ.1፡25-29)
እግዚአብሔር በተለይ በወንድማችን ጳውሎስ በኩል በተሰበከው ወንጌል የገለጠው ምሥጢር አንድ ነው። እርሱም የጽድቅ ዘር የሆነው ክርስቶስ በእኛ ውስጥ መሆኑንና በሕይወት አካሄዳችንም የኑሮአችን ፍሬ ሆኖ የሚገለጠው ክርስቶስ ራሱ መሆኑን ነው። የተወደደው ሐዋርያ ይህንን የጽድቅ ዘር በወንጌሉ የዘራባቸውን ቅዱሳን “እናንተ የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ” እያለ፤ ክርስቶስ በእነሱ እስኪሳል ወይም ሕያው ሆኖ እስኪገለጥና የሕይወት አካሄዳቸው ደግሞም የኑሮቸው ፍሬ እስኪሆን ድረስ ዕለት ዕለትእንደ ትጉ ገበሬ አገልግሎቱን ይፈጽም ነበር። የተጋድሎውንም ዓላማ "በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰው ማቅረብ" ብሎታል። ይህም የመንፈሳዊው ገበሬ የድካሙ የመጨረሻ ውጤት ወይም ፍሬው ነው።
“ስለ እናንተ እንደ ተሰጠኝ እንደ እግዚአብሔር መጋቢነት፥ የእግዚአብሔርን ቃል ፈጽሜ እንድሰብክ እኔ የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ሆንሁ። ይህም ቃል ከዘላለምና ከትውልዶች ጀምሮ ተሰውሮ የነበረ ምሥጢር ነው፥ አሁን ግን ለቅዱሳኑ ተገልጦአል። ለእነርሱም እግዚአብሔር በአሕዛብ ዘንድ ያለው የዚህ ምሥጢር ክብር ባለ ጠግነት ምን እንደ ሆነ ሊያስታውቅ ወደደ፥ ምሥጢሩም የክብር ተስፋ ያለው ክርስቶስ በእናንተ ዘንድ መሆኑ ነው። እኛም በክርስቶስ ፍጹም የሚሆን ሰውን ሁሉ እናቀርብ ዘንድ ሰውን ሁሉ እየገሠጽን ሰውንም ሁሉ በጥበብ ሁሉ እያስተማርን የምንሰብከው እርሱ ነው። ለዚህም ነገር ደግሞ፥ በእኔ በኃይል እንደሚሠራ እንደ አሠራሩ እየተጋደልሁ፥ እደክማለሁ።” (ቆላ.1፡25-29)